የወርቃማ ሰኞ መርሃ ግብር ተካሄደ

image description
- In Training    0

የወርቃማ ሰኞ መርሃ ግብር ተካሄደ

ITDB፦ህዳር 22/2018 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሳምንታዊው የወርቃማ ሰኞ መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡ በዚህ መርሃ ግብር ላይ የቢሮው አመራሮች፣ ዳይሬክተሮች እና ባለሙያዎች የተገኙ ሲሆን የቢሮ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ዲዛይን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ሚካኤል በራስ መተማመን እጦት፣ የሚያስከት ጉዳት፣ ህክምናዉ ላይ ሰፊ ማብራርያ ሰጥተዋል።

በመጨረሻም የቢሮ ሀላፊ አቶ አዋሌ መሀመድ በራስ መተማመንና አመራርነት ከራስ እንደሚጀምር እንዲሁም ስራችንን በአግባቡ በመስራት ከጠባቂነት መንፈስ መላቀቅ እንደሚገባ በማመላከት በሳምንቱ የሚከናወኑ ተግባራት ዝርዝር በመማመላከት መርሃ-ግብሩ ተጠናቋል።

ወቅታዊና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ዌብ ሳይት (website):https://www.aaitdb.gov.et ፌስቡክ (Facebook page):https://www.facebook.com/AAITDB

ኢሜይል (Email): aaitdb@aaca.gov.et

መስመር ስልክ (Phon Number):+251-118547714


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments